እንኳን በሰላም መጡ!!

   ይህ የሶስቱ መለአከ መልዕክት የወንጌል አገልግሎት ነው።

የዚህ አገልግሎቱ ዋና ተልዕኮ ትክክለኛ የወንጌልን እውነት ለሀገራችን ህዝቦች በሙሉ ማዳረስ ሲሆን በማንም ቤተ-ክርስትያን ተኖ ስር ያልሆነና ሁሉም የሀገራችን ህዝቦች የክርስቶስ ደቀ መዝሙር እንዲሆን ማስቻል ነው:: 

በአለማችን ላይ እየተካሄደ ያለ ታላቅ

ጦርነት እንዳለ ያውቃሉ? ይህ ጦርነት

ግን የሚደረገው በሃገራት መካከል

ወይም በሁለት ሰዎች መካከል የሚደርግ

ጦርነት አይደለም። ነገር ግን

በክርስቶስና በሰይጣን መካከል፣

ነፍሳትን ለማዳንና ለማጥፋት የሚደረግ

ትንቅንቅ ነው:: ይህ ደግሞ ሁሉንም

ሰው የሚያካትት ነው:: 

በምድርም ለሚኖሩ ለሕዝብም ለነገድም ለቋንቋም ለወገንም ሁሉ ይሰብክ ዘንድ የዘላለም ወንጌል ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ መካከል ሲበር አየሁ፤በታላቅ ድምፅም። የፍርዱ ሰዓት ደርሶአልና እግዚአብሔርን ፍሩ ክብርንም ስጡት፤ ሰማይንና ምድርንም ባሕርንም የውኃንም ምንጮች ለሠራው ስገዱለት አለ። ራዕ 14:6-7

እነሆ ዛሬ ህይወትንና በረከትን ሞትንና ጥፋትን በፊትህ አኑሬአሁ፡፡ አምላክህን እግዚአብሔርን እንድትወድ በመንገዱም እንድትሄድና ትእዛዙን፤ ሥርአቱንና ህጉን እንድትጠብቅ አዝሃለሁ ከዚያም በህይወት ትኖራለህ፤ ትበዛለህም አምላክህም እግዚአብሔር ትወርሳት ዘንድ በምትገባነት ምድር ይባርክሃል፡፡ ዘዳግ 30፡15